በልደታ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ዋና ዋና ተግባራቶች

1. በሀብት ማሰባሰብና አቅም ማጎልበት ቡድን የሚሰጡ አገልግሎቶች
  • ጥናት ማካሄድ፣
  • ለማህበረሰብ አቀፍ አደረጃጀቶች ንቅናቄ መፍጠር ፣
  • ለብሎክ ነዋሪዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት፣
  • አማራጭ የፋይናንስ ምንጭ መፈለግ፣ ፕሮጀክት ማበልጸግ፣ ሀብት ማሰባሰብ እና ማከማቸት፤፤
  • በብሎክ አደረጃጀት ላይ የሚነሱ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች በመለየት ከሚመለከተው አካል ጋር እንዲፈታ ማመቻቸት፤
2. በሰላም እሴት ግንባታ ቡድን የሚሰጡ አገልግሎቶች
  • በብሎክ የደንብ ጥሰት ሊፈጥሩ የሚችሉ ጉዳዮችን በመለየት እርምጃ እንዲወሰድ ማስደረግ፤
  • የብሎክ አደረጃጀትን በመጠቀም ሰላምና ጸጥታን የተመለከተ ወቅታዊ የመረጃ ልውውጥ ማድረግ፤
  • የብሎክ አደረጃጀትን በመጠቀም ህገ-ወጥ ተግባራትን መከላከል፤
  • በህብረተሰብ ተሳትፎ የአካባቢን ሰላምና ደህንነት መጠበቅ፤
3. በመሠረተ ልማት ቅንጅት ቡድን የሚሰጡ አገልግሎቶች
  • የግንባታ ዲዛይን ማዘጋጀት፤
  • የጨረታ ውለታ ማስተዳደር፤
  • የሚገነቡ መሰረተ ልማቶች ክትትልና ቁጥጥር ማድረግ፤
  • የሚገነቡ የመሰረተ ልማት ሥራዎች መረከብና ማስተዳደር፤
  • የብሎክን እና የመሰረተ ልማት መረጃን መሰብሰብና ማደራጀት፤

4. በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ቡድን የሚሰጡ አገልግሎቶች
  • የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማሰተባበር፤
  • የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ግንዛቤ እና ማስረፅ፤
  • የበጎ ፈቃድ ካውንስል ማሳተፍ፤
  • ለበጎ ፈቃድ የተሰበሰበውን ሀብት ማሰራጨት፤
  • በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዙሪያ ክትትልና ቁጥጥር ማድረግ፤
  • ደረጃ በህብረተሰብ ልማትና በበጎ ፈቃድ ተግባር ለተሳተፉ እውቅናና ማበረታቻ መስጠት፤
  1. ገጽ-1
  2. ገጽ-2